በእየሩሳሌም አስራት ላይ የደረሰውን ግድያ ዝም ብለን አናልፍም!

እየሩሳሌም አስራት በህዳር 13 ቀን 2016 በፖሊስ አባል በተተኮሰ ጥይት ጀርባዋ ላይ ተመትታ ከሶስት ቀናት በኋላ በደረሰባት ጉዳት ምክንያት ህይወቷ አልፏል። ጉዳዩን የዘገቡት አሃዱ ሬድዮ እና ቲክቫ ጥቃቱ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ቀበሌ 25 መሆኑንና ተጠርጣሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንደዋለ ገልጸዋል።
የሴቶች በተለያዩ ጊዜያት ለተለያዩ ጥቃቶች መጋለጥና ለህይወት ህልፈት መዳረግ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተበራከተ የመጣ ድርጊት ሆኗል። በተለይም ደግሞ የህግ ማስፈጸም ሃላፊነት በተሰጠውና ለዜጎች ከለላ መስጠት በሚገባው የፖሊስ አባል ይህ ወንጀል በመፈጸሙ ከልብ ማዘናችንን እንገልጻለን።

በጸጥታ አባላት በማንአለብኝነት የሚገደሉ ሴቶችን አሳዛኝ ዜናዎች በተጋጋሚ እየሰማን መሆኑ አስደንጋጭና አሳሳቢ ጉዳይ ሆኗል። ይህ ወንጀል በአንድ ግለሰብ ላይ ብቻ የተፈጸመ ወንጀል አይደለም፤ ጉዳዩ የፖሊስን የህዝብ አገልጋይነት፣ ተዓማኝነት እና አጠቃላይ ምስል ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ነው። በተጨማሪም የተፈጸመው ወንጀል የሴቶች ከጥቃት የመጠበቅና ከለላ የማግኘት የመብት ጥያቄዎችን ድርጊት የበለጠ ስጋት ውስጥ ያስገባ ነው።

የፌደራል ፖሊስና የጸጥታ አካላት አባላቶቻቸውን የመመልመልና የማሰልጠን ተግባራቸውን አንዲያጤኑ፤ በአባላቶቹ እና ተቋሙ ላይ ከባድ የፍተሻ፣ የምዘና፣ የቁጥጥርና የዲስፕሊን ማስተካካያ እርምጃ ሊያደርግ እንደሚገባ እየገለጽን ፤ ፖሊስ ተጠርጣሪው የፖሊስ አባል የፈጸመውን የወንጀል ድርጊት በህይወት የመኖር መሰረታዊ ህገመንግስታዊ መብትን ከመጣሱም በላይ ህገመንግስቱን መሰረት በማድረግ የወጡግ የህገመንግስቱን መርሆች እና ህግጋቶችን የፌደራል ፓሊስ አባላት ሚኒስቴር ካውንስል መተዳደሪያ ደንብ 260/2012፣ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ 720/2011 እና የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አዋጅ 313/2003 እንዲሁም የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን መተዳደሪያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ 86/2003ን የሚጣረስ ድርጊት በመሆኑ አጽንዖት በመስጠት ይህ የፖሊስ አባል ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኝ የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ ለፍትህ ስርዓቱ አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ እና የፖሊስ ኮሚሽኑ ደግሞ በልዩ ሁኔታ ያላሰለሰ እና ቀጣይነት ያለው ትብብር እንዲያደርግ እንዲሁም በአግባቡ ሃላፊነቱን እንዲወጣ እንጠይቃለን፤ እናሳስባለን።

የፍትህ ሚኒስቴር፣ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ፣ የሰብዓዊ መብቶች እና የሴቶች መብቶች ተቋማት እንዲሁም የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጉዳዩን በከፍተኛ ደረጃ እንዲመለከተው እና ማንም ሰው ፖሊስን ጨምሮ ከህግ በታች መሆኑኑን እንዲያረጋግጥና ለእየሩሳሌም አስከፊ ሞት ግልጽና ተገቢው የፍትህ ምላሽ እንዲሰጥ እንጠይቃለን።

ፈራሚ ድርጅቶች
1. ሴታዊት ንቅናቄ
2. ኢምፓቲ ፎር ላይፍ ኢንተግሬትድ ደቨሎፕመንት አሶሴሽን (ኤሊዳ)
3. አዲስ ፓወርሃውስ
4. ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች በኢትዮጰያ
5. የኢትዮጵያ ሴት የህግ ባለሙያዎች ማህበር (EWLA) 
6. የኢትዮጵያ ሴቶች መብት ተሟጋች (EWRA)
7. የኢትዮጵያ የመብት ተሟጋቾች ማዕከል (EHRDC)


የአዲስ ዓመት የሰላም ጥሪ

በመገባደድ ላይ የሚገኘው 2015 ለአገራችን ኢትዮጵያ ሁለት ገጽታዎች አሉት፤ በአንድ በኩል የሰላም ጅምር ተስፋ ይዞ ቢመጣም፥ በሌላ በኩል ደግሞ ግጭቶች ተባብሰው በዜጎች ሕይወትና የአገር ሀብት ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን የዚህ የሰላም እጦት ዳፋም ለመጪው አዲስ ዓመት ሊያወርስ ዋዜማው ላይ እንገኛለን።

እኛ ሥማችን ከዚህ የሰላም ጥሪ ግርጌ የተዘረዘረው አገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ከአገራችን ወቅታዊ ሁኔታዎች ጋር በተያያዘ በሰላም፣ ዴሞክራሲ እና ሰብዓዊ መብቶች ላይ የተለያዩ ሥራዎችን ከመሥራት ባሻገር፣ በተናጠልም ይሁን በጋራ የተለያዩ ይዘት ያላቸውን መግለጫዎች እና ጥሪዎች ስናደርግ መቆየታችን የሚታወስ ነው። ከነዚህም ጥሪዎች መካከል አምና እና ካቻምና በአዲስ ዓመት ዋዜማ ያወጣናቸው የሰላም ጥሪዎች የሚታወሱ ናቸው። መጪው አዲስ ዓመት መንግሥት ሁሉን ዐቀፍ የሰላም መድረክ በመፍጠርና ግጭቶችን በመከላከል፣ የሰላም እጦቱ በዘላቂነት የሚፈታበት የአጭር፣ የመካከለኛ፣ እና የረዥም ጊዜ መፍትሔዎች የሚቀየሱበት እንዲሆን ጥሪያችንን እንደሚከተለው እናቀርባለን።

ያሳለፍነው ዓመት መባቻ የትግራይ ክልል ጦርነት የተፋፋመበት የነበረ ቢሆንም፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ በተደረገው የፕሪቶሪያ የሰላም ንግግር ለሁለት ዓመታት የዘለቀው እና ብዙ ሰብዓዊ እልቂት እና ቁሳዊ ውድመት ያስከተለው ግጭት ከጥቅምት 23፣ 2015 ጀምሮ በሰላማዊ መፍትሔ እንዲጀመር አስችሏል። ይህም ፈቃደኝነቱ ካለ የትኛውንም ዓይነት ግጭት በሰላም ለመፍታት እንደሚቻል ትምህርት ሰጥቷል ብለን እናምናለን። ይሁንና ዘንድሮም እልባት ያልተገኘላቸው ግጭቶች በአገሪቱ የተለያዩ ክልሎች ያሉ ሲሆን፥ በዚሁ ዓመት የተስተዋሉ አዳዲስ እና ነባር ግጭቶች በመጪው ዓመትም ተባብሰው እንዳይቀጥሉ ያሰጋል።

በኦሮሚያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች ከሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ኃይሎች ጋር የቀጠለው ውጊያ፣ በአማራ ክልል ከየልዩ ኃይሉን መፍረስ ጋር ተከትሎ ከታጠቁ ኃይሎች ጋር የተቀሰቀሰው እና ተባብሶ የቀጠለው ግጭት፣ እስከ አሁንም ድረስ ምርጫ ማካሔድ ያልተቻለበት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ ያለው አለመረጋጋት፣ በጋምቤላ ክልል ተደጋግሞ የሚስተዋለው የእርስ በርስ ግጭትና አለመረጋጋት፣ ከደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል መልሶ መዋቀር ጋር የተያያዙ ሕዝባዊ ቅራኔዎች እና ተቃውሞዎች፣ በኦሮሚያ ክልል የተካሄዱ አስተዳደራዊ መዋቅር ለውጦች ያስከተሉት ግጭት፣ መፈናቀል፣ ቅራኔና ተቃውሞዎች፣ በቤተ እምነቶች እና የፖለቲካ መሪዎች የተከሰቱ ውጥረቶች፣ በዜጎች የመንቀሳቀስ መብት ላይ የተጣሉ ገደቦች፣የጅምላና የዘፈቀደ እስሮች፣ የጋዜጠኞች እና የመብቶች ተሟጋቾች መዋከብና እስራት፣ የአስገድዶ መሰወር ድርጊቶች፣ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ግድያ፣ ያለመከሰስ መብት ያላቸውነ የሕዝብ ተወካዮች ማሰር፣ በጥቅሉ የፖለቲካ ምኅዳሩን የሚያጠቡ ሁኔታዎች ያገባደድነው ዓመት ኹነቶች ጥቅል ገጽታዎች ናቸው።

እነዚህ ኩነቶች እንዳሉ ሆኖ በኦሮሚያ ክልል የቀጠለውን ግጭት ለማስቆም የተደረገው የዛንዚባሩ የሰላም ድርድር ጅምር ሙከራ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና በጋምቤላ ክልሎች ከሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ሀይሎች ጋር የተደረጉ አንዳንድ ሥምምነቶችም ተስፋ ሰጪ ጅምሮች ነበሩ። ከነዚህ በተጨማሪ ፣ በሽግግር ፍትሕ ዙሪያ በፖሊሲ አማራጮች ላይ ውይይቶች መካሔዳቸው እና ለሕዝባዊ አስተያየት መቅረቡ እንዲሁም ለአገራዊ ምክክር የተሳታፊዎች ልየታ እና አጀንዳ ማሰባሰብ በሀረሪ፣ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እና ሲዳማ እንዲሁም ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር መጀመራቸው አዎንታዊ እርምጃዎች ናቸው። እነዚህ ጅምሮች ትኩረት አግኝተው ሰላማዊ መፍትሔዎች የበለጠ ተቀባይነት እንዲያገኙ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቁርጠኝነት እና ጠንካራ ሥራ ያስፈልጋል።

መጪው የ2016 ዓመት ከላይ የጠቀስናቸውን እና የዜጎችን መሠረታዊ የሰብዓዊ መብቶች እና ነጻነቶች የሚያጣብቡ ግጭቶች የሚቀጥሉበት እንዳይሆን በማሰብ በግጭቶች ውስጥ ለሚሳተፉ አካላት እና ደጋፊዎቻቸው፣ ለመንግሥት ኃላፊዎች፣ ለፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ለሲቪክ ማኅበራት፣ ለመገናኛ ብዙኃን እና ጋዜጠኞች፣ ለምሁራን፣ ለተፅዕኖ ፈጣሪዎች፣ ለእምነት ተቋማት መሪዎች እና ለዓለማቀፉ ማኅበረሰብ ጥሪያችንን እንደሚከተለው እናቀርባለን።

1ኛ) አገር ዐቀፍ የሰላም መድረክ ይመቻች!
ብዙዎቹ ነውጥ አዘል ግጭቶች የተቀሰቀሱትም ይሁን የተባባሱት ውጥረቶችን በፖለቲካዊ ንግግር እና ምክክር ሳይሆን በኃይል የመፍታት የቆየ ባሕል በመኖሩ ነው ብለን እናምናለን። ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ሁሉንም የማኅበረሰብ አካላት የሚያሳትፍ አገር ዐቀፍ የሰላም መድረክ (የሰላም ኮንቬንሽን) ተመቻችቶ የአጭር ጊዜ፣ የመካከለኛ ጊዜ እና የረዥም ጊዜ ግጭትን የመከላከል፣ የመፍታት እና የሰላም ግንባታ ሥራዎች የሚጠናከሩበት አገራዊ ፍኖተ ካርታ እንዲዘጋጅ፤

2ኛ) ገለልተኛ ምርመራና ተጠያቂነት ይስፈን!
ተጎጂዎችን ማዕከል ያደረገ (victim centered) የተጠያቂነት ስርዓት መስፈን በሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች እና በግጭቶች ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ፍትሕ የሚሰጥ ከመሆኑም ባሻገር፥ የበቀል አዙሪትን ለመግታት እና ለፍትሕ ተቋማት ተዓማኒነትም ዋልታ ነው ብለን እናምናለን። ለነውጥ አዘል ግጭቶች መንስዔ የሆኑ፣ ሕዝባዊ እና ብሔራዊ ጥቅምን የሚጎዱ እና ሕጋዊ መሠረት የሌላቸው ውሳኔዎችን ያሳለፉ፣ በነውጥ አዘል ግጭቶች ውስጥ በመሳተፍ ንፁኃንን ያጠቁ፣ የጥላቻ ንግግሮችን እና ግጭት ቀስቃሽ ንግግሮችን በአደባባይ ያደረጉ እና ንፁኃንን ለጥቃት ያጋለጡ አካላት በነጻ እና ገለልተኛ የፍትሐዊ የምርመራ እና የዳኝነት ሒደት ተጠያቂ እንዲደረጉ፣ የተጀመረው የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ በሐቀኝነት እና ሕዝባዊ ተቀባይነት ባለው መንገድ ወደ ተግባር እንዲገባ፤ በሒደቱም የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እና ዓለም ዐቀፍ ድጋፍ ሰጪ ባለሙያዎች እንዲሳተፉ፤

3ኛ) ፆታዊ ጥቃቶች ተገቢው ትኩረት ይሰጣቸው!
በነውጥ አዘል ግጭቶች ወቅት እና አለመረጋጋት ባለባቸው ሁኔታዎች ሴቶች እና ሕፃናት ላይ የሚፈጸሙ ፆታዊ ጥቃቶች መጠናቸው የሚጨምር ሲሆን፥ በአገራችንም ችግሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መጥቷል። ይሁንና የችግሩን አሳሳቢነት የሚመጥን ትኩረት አልተሰጠውም። ስለሆነም ጥቃቶቹን ለመከላከል፣ ለተጎጂዎችም የጤና እና ሥነ ልቦና ድጋፍ ለመስጠት፣ የጥቃቶቹን ፈፃሚዎች እና ተባባሪዎች ለሕግ ተጠያቂነት ለማቅረብ የፖሊሲ አቅጣጫዎች እንዲቀመጡ እና በቂ እርምጃዎች እንዲወሰዱ፣ ጉዳዩ በተለይ የሚመለከታቸው መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችም ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ፤

4ኛ) የተጋላጭ እና ግፉአን ጥበቃ ማዕቀፍ ይዘርጋ!
ነውጥ አዘል ግጭቶች በተከሰቱ ቁጥር የከፋ ሰቆቃ እና ጥቃት የሚደርስባቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች ኅዳጣን (minorities)፣ እንዲሁም ለጥቃት እና መድልዖ ተጋላጭ (vulnerable) ቡድኖች፤ በተለይም ሴቶች፣ ሕጻናት፣ የአካል ጉዳተኞች እና አረጋዊያን እና ግፉዓን (marginalized) የሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች ናቸው። ለነዚህ የማኅበረሰብ ክፍሎች ተገቢውን እና ልዩ ጥበቃ ማድረግ የሚያስችሉ አገራዊ፣ ሕጋዊ እና ተቋማዊ ማዕቀፍ እና አሠራሮች እንዲዘረጉ፤

5ኛ) ሕዝባዊ ተሳትፎ ይረጋገጥ!
በርካታ ግጭቶች እየተቀሰቀሱ ያሉት በፌዴራሉ እና ክልሎች መንግሥታዊ መስተዳድሮች የሚወሰኑ ውሳኔዎች የዜጎችን ትርጉም ያለው ተሳትፎ (meaningful participation) ያላረጋገጡ እና የብዙኃንን ይሁንታ ያላገኙ በመሆናቸው ነው ብለን እናምናለን። ስለሆነም፣ ሁሉም የመንግሥት አካላት መዋቅራዊ ለውጦችን በማድረግ፣ ማኅበረሰቦች ዘንድ ቅሬታ እና ጥርጣሬ ሊፈጥሩ የሚችሉ እርምጃዎችን ከመውሰዳቸው በፊትና ውሳኔዎችንም ከመወሰናቸው በፊት፣ ምክረ ሐሳቦቻቸውን ከባለድርሻ አካላት ጋር በግልጽ በመወያየት እና በሰፊ ሕዝባዊ ተሳትፎ የብዙኃንን ይሁንታ በቅድሚያ እንዲያገኙ፤

6ኛ) የቅድመ ግጭት መጠቆሚያ እና መከላከያ ስርዓት (early warning system) ይኑር!
ቅሬታዎች ወደ ነውጥ የሚሸጋገሩበት ሒደት በተደጋጋሚ ቀድሞ የሚስተዋል መሆኑን እስካሁን ኢትዮጵያ ከገጠሟት ጦርነቶች እና ነውጥ አዘል ግጭቶች ትምህርት መውሰድ ይቻላል። ስለሆነም፣ ወደ ነውጥ አዘል ግጭቶች ሊሸጋገሩ የሚችሉ ውጥረቶችን ቀድሞ በመገምገም ግጭት መጠቆሚያ (alerting) እና መከላከያ ሥራዎች የሚከናወኑበት ስርዓት በመዘርጋት መንግሥት ግዴታውን እንዲወጣ፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ተቋማት እና ዓለም ዐቀፍ ድርጅቶችም በግጭቶች እየደረሱ ያሉ ተጨማሪ ጉዳቶችን ለመከላከል በቂ ትኩረት ሰጥተው እንዲሠሩ፤

7ኛ) የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት ሳይስተጓጎል ይቀጥል!
በጦርነትና በተለያዩ ክልሎች በተከስቱ ግጭቶች ከቀያቸው የተፈናቀሉ፣ ቤትና ንብረታቸው የወደመባቸው፣ በዚሁም ምክንያት በተፈናቃዮች የመጠለያ ካምፖች የሚገኙ እና ለርሃብና እርዛት የተጋለጡ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች አፋጣኝ፣ የማይስተጓጎል እና በቂ የሆነ የምግብ፣ የጤና አገልግሎት እና ሌሎች መሠረታዊ አቅርቦቶች፣ በዘለቄታውም የመልሶ ማቋቋም ድጋፍ በማናቸውም ሁኔታ ሳይገደቡ እና ሳይቆራረጡ በሚመለከታቸው አካላት ሊቀርቡላቸው ይገባል። ዓለም ዐቀፍ የሰብዓዊ ድጋፍ አቅራቢ ድርጅቶች በድጋፍ አሰጣጥ ሒደት ላይ የሚገጥሟቸውን አስተዳደራዊም ሆነ ሌሎች መሰናክሎች ምክንያት በማድረግ በአስከፊ ሁኔታ ላይ ለሚገኙ የጥቃት ጉዳተኞች ድጋፍ ጠባቂዎች የሚያቀርቧቸውን ድጋፎች ሳያስተጓጉሉ እንዲቀጥሉ፤ በሒደቱ ለሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች መንግሥት ተገቢውን አስተማማኝ የተጠያቂነት ስርዓት እንዲዘረጋ፤

8ኛ) የጥላቻ ንግግር እና የተዛቡ መረጃዎች ስርጭት ይቁም!
የጥላቻ ንግግሮች እና ግጭት ቆስቋሽ መልዕክቶች ነውጥ አዘል ግጭቶችን የሚያዋልዱ እና የሚያፋፍሙ መሆናቸውን ባለፉት ዓመታት አስተውለናል። የፖለቲካ ልኂቃን፣ የመንግሥት ኃላፊዎች፣ የብዙኃን መገናኛ ተቋማት፣ የማኅበራዊ ሚዲያ አቀንቃኞች እና ሌሎችም የተዛቡ መረጃዎችን ከማሰራጨት፣ ብሎም ሕዝብን በጅምላ ከሚፈርጁ ወይም ግጭቶችን ከሚቆሰቁሱ እና ከሚያባብሱ የቋንቋ አጠቃቀሞች እና መልዕክቶች ራሳቸውን እንዲቆጥቡ፤

9ኛ) የሲቪክ ምኅዳሩ ጥበቃ ይደረግለት!
የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች እና ጋዜጠኞች፣ እንዲሁም የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች እና ሚዲያዎች በሥራዎቻቸው ሳቢያ የዘፈቀደ እስር፣ ማሰቃየት፣ አስገድዶ መሰወር፣ ሞት እና ሌሎችም የማዋከብ ድርጊቶች እየተፈፃሙባቸው ይገኛል። ይህም በሕግ የተሰጣቸውን ሐሳብን የመግለጽ፣ የመደራጀት፣ እና የመሰብሰብ መብቶቻቸውን የሚያፍን እና የሥራ ኃላፊነታቸውን እንዳይወጡ የሚያደናቅፍ በመሆኑ የሚዲያ እና ሲቪክ ምኅዳር በቂ ጥበቃ እንዲደረግለት መንግሥት ሕገ መንግሥታዊ ግዴታውን እንዲወጣ፤

10ኛ) ባለድርሻ አካላት ለሰላም ግንባታ የበኩላቸውን ይወጡ!
ሰላም የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ትብብር የሚፈልግ በመሆኑ፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ መገናኛ ብዙኃን፣ ዓለም ዐቀፉ ማኅበረሰብ፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ እምነት ተኮር እና ማኅበረሰብ ዐቀፍ ተቋማት እንዲሁም ባሕላዊ ተቋማት በቅንጅት እና በተናጠል የሚጠበቅባቸውን በማድረግ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

እኛም የዚህ የሰላም ጥሪ አቅራቢዎች የታመቁ ቅራኔዎች ወደ ነውጥ እንዳይሸጋገሩ ለመከላከል፣ ነውጥ አዘል ግጭቶች በሰላማዊ ንግግሮች እንዲፈቱ፣ እንዲሁም የሰላም ጅምሮች ሁሉን አካታች እና ዘላቂ እንዲሆኑ የድርሻችንን አስተዋፅዖ ለማበርከት፤ እንዲሁም ከላይ ባቀረብናቸው ጥሪዎች መሳካት ላይ አስፈላጊ የሆኑ ተግባራዊ ሥራዎችን ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር ለመሥራት ዝግጁ መሆናችንን ለመግለጽ እንወዳለን።

አዲሱ የ2016 ዓመት ለችግሮቻችን ሁሉ ሰላማዊ እና ዘላቂ መፍትሔ የምናበጅበት፣ ግጭቶች የተወገዱበት፣ ሰብዓዊ መብቶች በአግባቡ የሚከበሩበት፣ ለጉዳት ተጋላጭ የሆኑ ዜጎች ሙሉ ጥበቃ የሚያገኙበት፣ የጥላቻ ንግግሮች የሚቆሙበት፣ የሕግ የበላይነት የሚረጋገጥበት፣ ለሰላም ግንባታ እና ለዲሞክራሲያዊ ስርዓት መስፈን የዜጎች ንቁ ተሳትፎ የሚታይበት እንዲሆን መልካም ምኞታችንን እናቀርባለን።
መልካም አዲስ ዓመት!

የዚህ የአዲስ ዓመት የሰላም ጥሪ አቅራቢ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የሚከተሉት ነን፤
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ህብረት (CEHRO)
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (EHRCO)
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል (EHRDC)
የመብቶችና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (CARD)
ስብስብ ለሰብዓዊ መብቶች በኢትዮጵያ (AHRE)
የኢትዮጵያ ሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር (EWLA)
የሕግ ባለሙያዎች ለሰብዓዊ መብቶች (LHR)
ሴታዊት ንቅናቄ
ኢንተርአፍሪካ ግሩፕ (IAG)
የኢትዮጵያ ሴቶች መብቶች ተሟጋች (EWRA)
የኢትዮጵያ ሴቶች ማኅበራት ቅንጅት (NEWA)
የኢትዮጵያ ሰራተኞች መብት ተሟጋች (ELRW)
ሁሉን ዐቀፍ ራዕይ ለዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ (IVIDE)
ኢስት አፍሪካን ኢኒሼቲቭ ፎር ቼንጅ (I4C)
የሴቶች ህብረት ለሰላምና ለማህበረሰብ ፍትህ (WAPSJ)
ልማት ለሁሉም (DFA)
አዲስ ፓወርሃውስ (APH)
ኢትዮጵያዊ ተነሳሽነት ለሰብዓዊ መብቶች (EIHR)
ጉድ ሳማሪታን ማህበር (GSA)
ሲቄ ዉሜንስ ዴቨሎፕመንት አሶስዬሽን (SWDA)
ሴቶች ይችላሉ ማኅበር (WCDI)
ሙጀጀጓ ሎካ የሴቶች ልማት ማኅበር (MLWD)
ሳራ ፍትሕ ከሁሉም የሴቶች ማኅበር
የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኛ ሴቶች ብሔራዊ ማኅበር (EWDNA)
ኢንሃንስድ ቻይልድ ፎከስድ አክቲቪቲስ (ECFA)
ሚዛን ወጣት የሕግ ባለሙያዎች ማዕከል
ሰላም ለኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ድርጅት
መልካም እጆች ለሰላም፣ ዲሞክራሲ እና ሰብአዊ መብት ግንባታ
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሙያ ሴቶች ማህበር
ሚዛን የጋዜጠኞች ሞያ ምሩቃን ማኅበር
​መልካም አስተዳደር ለአፍሪካ-ምሥራቃዊ አፍሪካ (GGA-EA)
የሰብአዊ መብቶች እና ሰላም ግንባታ ማዕከል (CPHRPB)
ተስፋ ለሕፃናት ማኅበር (HFCA)
ድሬ የተናጀ የማኅበረሰብ ልማት ድርጅት
ሆፕፉል ጄኔሬሽን ፎር ዴቨሎፕመንት

English version can be found here


Timeline of Setaweet's activities relating to conflicts (November 2020 - June 2023)

Misikir documentary
June 2022 - July 2023

Trauma-centered Healing in Tigray
May 2023 - Ongoing

National Women’s Conference: focus on the importance of humanitarian aid, the need for reconciliation, empathy, and healing among women
April 2023

Reeyot Alemu's conversation with Sehin Teferra on women's participation in politics, GBV, and rape as a weapon of war in Ethiopia
January 2023

የ16 ቀናት የፀረ-ጾታዊ ጥቃት ዘመቻ #“አሁንም አልረፈደም!” የ2015 ሴታዊት ንቅናቄ መልዕክት
November 2022

Sehin Teferra’s Comments on CSO joint-call for Peace and Accountability on Addis Insight
October 2022

Fundraising for displaced mothers in Afar
The event showcased a documentary film - Aster Zaoude & Friends in partnership with Afar Pastoralist Development Association (APDA) present War and Displacement: Building Houses for people displaced by War in Afar 
September 2022

አስቸኳይ የሰላም ጥሪ ከአገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች
Joint Peace Call September 2022

News coverage of the call for peace
September 2022

Sehin Teferra's Commentary on Ethiopian Business Review - The End of the Beginning: The Charade of Representational Politics Needs to Give Way to Substantive Gains in Gender Justice
May 2022

Held meeting on the topic of Women and Conflict in Ethiopia - An overview of the situation of women in conflict and displacement setting in Ethiopia: a glimpse into a hidden world
April 2022

Position Statement of the Coalition for Women’s Representation in the Ethiopian National Dialogue
April 2022

Sehin Teferra's interview with Reeyot Alemu on Violence Against Women
February 2022

አዲስ ማለዳ ጋዜጣ ላይ የወጣ መልዕክት - የሴቶች ጥቃት የፖለቲካ ፍጆታ መሆኑ ይቁም!
November 2021 Addis Maleda newspaper Hidar 11 edition

የአዲስ ዓመት የሰላም ጥሪ ከአገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች
September 2021

Setaweet Launched #blanketdrive Campaign
June 2021

MeQenet Show’s episode on Sexual Violence within Conflicts
March 2021

Discussion on The Impact of Conflict on Women and Girls in Ethiopia
February 2021

Fundraiser for displaced women in Metekel zone in collaboration with NEWA
December 2020

Statement on the beginning of the conflict
November 2020

 


National Women's Conference 2023 Recap

The National Women's Conference, organized by Setaweet Movement with the support of Fredrich Ebert Stiftung (FES), took place on April 6 and 7 at Hilton Hotel. This conference, co-created with the Network for Ethiopian Women's Associations (NEWA), Timran, and Addis Powerhouse, is designed to bring different women's rights groups and human rights activities from across Ethiopia together, strengthen solidarity and create a national women's movement. We would like to extend our deepest gratitude to everyone who has supported this conference since its inception and look forward to a united movement that will be the voice for Ethiopian women.

 

Here is a brief summary of the two-day event. 

Day 1:

The National Women's Conference commenced with a blessing from community leaders in different languages, including Afan Oromo, Guragigna, and Amharic. The opening remarks were delivered by Sehin Tefera, Director of Setaweet, and Susanne Stollreiter, Resident Representative of Friedrich Ebert Stiftung. This was followed by a keynote speech from the guests of honor, Ethiopian Human Rights Commissioner for Women Meskerem Gesit, and Ethiopian National Election Board chairperson Birtukan Mideksa.

During the keynote speech, the following points were raised:

  • The purpose of discussing the traumas and challenges faced by women was not to disempower them, but to make them feel heard and understood. Emphasizing empathy and understanding the pain of survivors was crucial to building solidarity.
  • The need for adept politicization in times of conflict, while emphasizing the importance of depoliticizing suffering once the conflict is over. Politics should still play a role in addressing the needs of women, as empathy and understanding should be integrated into the political system.
  • The importance of including women's issues in the upcoming national dialogue and peacebuilding processes, and the need to ensure that women's voices are heard and their needs are addressed.

The day's agenda was introduced by Yemeserach Legesse, who served as the facilitator for the first day of the conference. This was followed by the launch of the Misikir documentary movie, which showcased stories of women from different conflict-affected areas and how the conflicts had impacted them and their families. A reflection and discussion session followed, with audience members expressing emotions, and gratitude for giving voice to these stories and inviting women to share their stories in upcoming episodes of Misikir documentary.

The next sessions focused on the situations of Ethiopian women in conflict-affected areas, with presentations from NEWA (Network of Ethiopian Women's Associations) and ELiDA (Empathy for Life in Integrated Development Association). Saba Gebremedhin, Executive Director of NEWA, presented the impacts of conflict on women, including the use of sexual violence as a tool during the war, economic and social impacts, and the need for gendered humanitarian responses to address these challenges.

Eyerusalem Solomon, the Executive Director of Timran, shared experiences on community dialogue and women's participation in the peacebuilding process, specifically in the upcoming national dialogue. She highlighted the importance of women's contributions to peacebuilding and their right to participate, citing examples of dialogues conducted by Timran in different regions of Ethiopia. The outcomes of these dialogues included a manifesto and peace walks in Addis Ababa, where groups from conflict-affected areas participated. Further, Timret (Civil Society Organizations involved in the national dialogue) by 50 civil CSOs focused on the need to include women in the peacebuilding and national dialogue processes. She highlighted the importance of raising women's issues, monitoring and advocating for women's participation, and creating awareness about how women can participate and present their issues in the national dialogue. Dialogues in regional areas, including with IDPs (Internally Displaced Persons), were also discussed, with clusters formed to facilitate grassroots discussions and equip women with knowledge for meaningful participation in the national dialogue and transitional justice processes.

Audience reflections included the need for leadership, structure, and strategy in building a women's movement, strategic inclusion of women's issues in the national dialogue, empowerment of women, safety for vulnerable women, networking, open discussions, strategic leadership, men's support, and inclusion of community and religious leaders in the peacebuilding efforts.

 

Day 2:

The second day of the conference was facilitated by Mulumebet Zenebe, Associate Professor at the Center for Gender Studies, Addis Ababa University. The day started with a Setaweet affirmation followed by a presentation on African Feminism by Hiwot Abebe from Setaweet. The presentation covered various topics such as the history of women in Ethiopia, approaches to African feminism, issues concerning African women, and the current state of the Ethiopian and African feminist movements.

After the presentation, there was a breakout session on the topic of "What feminist movement is and why we need it?" Reflections from the session included the lack of solidarity and control among organizations working on women's issues. Participants discussed the need to work together, set clear goals, assign responsibilities, advocate for women's rights, strategize advocacy efforts, change the term "feminist" to local languages, involve men in the movement, teach positive masculinity to children, focus on literacy and education, utilize youth voices, promote peacekeeping and conflict resolution, contextualize feminism, prioritize togetherness and mutual support, and take collective responsibility instead of blaming each other.

Dr. Mulumebet concluded the session by highlighting the importance of strategic planning, focusing on fundamental questions, innovative programs, and using digital tools. She emphasized the need for mutual support, problem-solving, and revising cultural systems that hinder progress, such as traditional views on God and luck.

Next, Hanna Lemma, founder and Director of Addis Powerhouse, gave a presentation on digital feminist movement building and young feminist networks. She discussed the principles of young feminist movement models, the pros and cons of digital feminism, and potential solutions for addressing the challenges social media poses for activists.

The conference also featured experiences shared by the Tesfaweet girls, who participated in a project under Setaweet aimed at addressing inequalities in access to education and opportunities for young married women through empowerment training. The girls expressed their gratitude for the project, which helped them become more assertive, communicate effectively with their husbands, and start their own businesses with proposed ideas. They shared that it was a great opportunity to be invited to Addis Ababa, as it was their first time leaving their community.

The Wizkids' workshop team also presented their efforts to cultivate gender equality among children through movies and the creation of the Yetibeb Lijoch Animation series, which they showcased through sample animation movies.

This was followed by a discussion on solidarity in movement, focusing on the importance of listening to each other, maintaining support even when physically apart, and avoiding competition among movements. Dr. Mulumebet emphasized the need for an effective mobilization strategy, stating that taking practical actions toward meeting our goals is necessary for solidarity and movement building. During the breakout session, participants emphasized the need for genuine care, prioritizing peace as a core problem to address. Participants grouped themselves according to what they identified to be urgent problems regarding women and conflict: gender-based violence, peacebuilding, food security, and the need for solidarity among women’s groups. Planning and strategizing, including separate plans for different religions, were also highlighted, along with building trust through mutual understanding and safe spaces for dialogue. The groups agreed to follow up on their plans by setting up telegram groups to discuss further activities. 

The conference concluded with closing remarks from Sehin Teferra, Director of Setaweet, who emphasized the need for concrete actions and assignments to continue the support and progress made during the conference. Participants reflected on the need to extend the movement to other regions and promised to host future meetings across the country.

In addition to the presentations, the conference also featured music and poetry performances by Tarik Asteraye, who delivered a monologue titled "Yeqaqqe Wuredot," Heran Tadesse, who presented a poem titled "Queen Sheba," and Lidya Woldekidan and Seble Aregawi, who performed music. Women-run businesses and artists also showcased their products during breaks for conference attendees. 


በሴቶች ላይ የሚፈጸምን የአሲድ ጥቃት በመቃወም በሴቶች መብት ተሟጋች ማህበራትና ድርጅቶች የተሰጠ የጋራ የአቋም መግለጫ


ቀን: ጥር 25/2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ

በሀገራችን የተለያዩ የሰብዓዊ መብትና የሴቶች ተቋማት በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች ለማስቀረት በርካታ ስራዎችን እየሰሩ መሆኑይታወቃል። ሴቶች ለጠለፋ፣ ያለዕድሜ ጋብቻ፣ አሰገድዶ መደፈር፣ ድብደባ፣ ግድያ እና የሌሎችም ጾታዊ ጥቃቶች ሰለባ መሆናቸው ግን አሁንም ቀጥሏል። ከቅርብ አመታት ወዲህ ደግሞ የአሲድ ጥቃት በተደጋጋሚ እየተፈጸመ የምናስተውለው በሴቶች ላይ የሚፈጸም አሰቃቂ የጾታዊ ጥቃት አይነት ሆኗል። በሀገራችን በዓመት ከ50 እስከ 70 በሚደርሱ ሴቶች ላይ ይህ ጥቃት እንደሚፈጸም መረጃዎች ያመላክታሉ። ይህንን ጥቃት በመቃወም የተለያዩ የሴቶች መብት ተሟጋች ተቋማት የተለያዪ የህግ ማሻሻያ የውትወታ ስራዎች እየሰሩ ይገኛሉ። ሆኖም ግን የአሲድ ጥቃት በሀገራችን ከጊዜ ወደ ጊዜ በተደጋጋሚ እየተፈጸመ መሆኑና ተመጣጣኝ እንዲሁም አግባብነት ያለው ምላሽ እየተሰጠ አለመሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት ተገቢው አትኩሮት እና ፍትሃዊ ምላሽ ሊሰጠው ይገባል የሚለውን
ለማሳሰብና ጥያቄያችንን ለማቅረብ ይህንን የጋራ አቋም መግለጫ አውጥተናል።

ይህ የአቋም መግለጫ በህዳር 10 ቀን 2015 ዓ. ም ከንብረት ማውደም እንዲሁም ተደጋጋሚ ዛቻ እና ማስፈራሪያ በኋላ በትዳር አጋሯ የአሲድ ጥቃት የተፈጸመባትን እና በጳውሎስ እና አቤት የሚባሉ ሆስፒታሎች ህክምና እየተከታተለች የምትገኘውን እና ደህንነቷን ከግምት ውስጥ በማስገባት ስሟ ያልተገለጸውን እህታችንን መነሻ በማድረግ የአሲድ ጥቃት በመቃወም የተሰጠ ነው።

የአሲድ ጥቃት በሀገራችን በተደጋጋሚ እየተከሰተ የመጣ በሴቶች ላይ የሚፈጸም ጥቃት መሆኑ አስደንጋጭና የማይካድ እውነት ነው። ወንጀሉ ከተራ አካላዊ ጥቃት (ጉዳት) የማስከተል ወንጀልነት በዘለለ ፆታን መሰረት ያደረገ ጥቃት መሆኑ በአብዛኛው በእህቶቻችን ላይ መፈጸሙ እሙን ያደርገዋል። በርካታ እህቶቻችን በዚህ ጥቃት ምክንያት ህይወታቸውን እና አካላቸውን ብሎም ህልም እና ማንነታቸውን ባላሰቡት እና ባልጠበቁት ሁኔታ አጥተዋል፤ እያጡም ይገኛሉ። ከአሲድ ጥቃት ያገገሙ ሴቶች ቀጣይነት ባለው የአካል ጉዳትና የሥነ ልቦና ቀውስ ጋር በመሆን ህይወታቸውን ለመምራት ይገደዳሉ። የአሲድ ጥቃት እንደ ህንድ ባሉ አንዳንድ ሀገሮች እንደሆነው ሁሉ የከፋ ጉዳት በሀገራችን ከማድረሱ በፊት መገታት ያለበት መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት መንግስት፣ የመብት ተቋማትና ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ይህንን አሰቃቂ ጥቃት ለማስቀረት የበኩላቸውን እንዲያደርጉ ጥሪያችንን ለማስተላለፍ እንወዳለን። ስለሆነም የአሲድ ጥቃት መሰረታዊ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ከመሆኑ ባለፈ የሚያሰከትለው አካላዊ፣ ሰነ-ልቦናዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበረሰባዊ ቀውስ ከፍተኛ መሆኑን በማስረገጥ የሚከተሉትን የጋራ አቋም መግለጫ እናስተላልፋለን፤

1ኛ) የፍትህ ሚኒስቴር የአሲድ ጥቃት ከአካላዊ ጥቃት በተጨማሪ ፆታዊ ጥቃት በመሆኑ በወንጀል ህጉ ውስጥ ራሱን በቻለ አንቀጽ እንዲሰፍር ሊያደርግ ይገባል፤
2ኛ) የጤና ሚኒስቴር የአሲድ ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች ከህክምናው ጋር በተያያዘ የሚያስፈልጋቸውን አገልግሎቶች መድሃኒቶችን ጨምሮ በነጻ እንዲያግኙ ህግ ማውጣት አለበት፤
3ኛ) ንግድ ሚኒስቴር እና ገቢዎች ሚኒስቴር የአሲድ አቅርቦት ላይ አስፈላጊ ደንብ በማርቀቅ በህጋዊ ፍቃድ ብቻ ሽያጭ የሚፈጸም እንዲሆንና ከታቀደለት አላማ አልፎ በእህቶቻችን ላይ ጥቃት መፈጸሚያ እንዳይሆን ክልከላ ሊያደርጉ ይገባል፤
4ኛ) ጤና ሚኒሰቴርና የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የአሲድ ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች ተገቢውን የማገገሚያ፣ የስነ-ልቦና፣ የህክምና፣ የኢኮኖሚያዊ እና ማህበረሰባዊ ድጋፍ የሚያገኙበት ሁኔታ ማመቻቸት ይኖርባቸዋል፤
5ኛ) ፍርድ ቤቶች ጥቃት አድራሾች ላይ ፈጣንና ተመጣጣኝ የህግ እርምጃ ሊወስድ ይገባል፤
6ኛ) የጸጥታ አካላት ጾታዊ ጥቃቶችን የመከላከል ስራዎቻቸውን አጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል፤ በተጨማሪም ማህበረሰቡ ጾታዊ ጥቃቶችን የመቃወም ባህሉን በማዳበር ማህበራዊ ሃላፊነታቸውን ሊወጡ ያስፈልጋል።

ይህንን የጋራ የአቋም መግለጫ ያስተላለፍን የሴቶች መብት ተሟጋች ተቋማት ኃላፊነታችንን አጠናክረን የምንወጣ ሲሆን ይህ ጥሪ የደረሳችሁ ሁላችሁም በሴቶች ላይ የሚፈጸምን ጥቃት ለማስቀረት ለምታሳዩት አንድነትና ለምታደርጉት ትብብር እናመሰግናለን።

የዚህ የጋራ የአቋም መግለጫ ፈራሚዎች ከታች ያሉ ተቋማትና ማህበራት ናቸው።
1. ሴታዊት ንቅናቄ
2. ሲቄ ውመንስ ድቭሎፕመንት አሶሲዬሽን
3. የኢትዮጵያ ሴቶች ማህበራት ቅንጅት
4. አዲስ ፓወር ሀውስ
5. የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል
6. የኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር
7. ሴታሴት
8. የኢትዮጵያ ሴት ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ጥምረት


Press Release: Improperly imprisoned EHRCO workers should be released immediately!

December 07, 2023
Addis Ababa

The Ethiopian Human Rights Council (EHRCO) on a statement issues on December 05, 2023 announced that EHRCO sent experts to investigate the matter based on the petition submitted to the Ethiopian Human Rights Council (EHRCO) by the people whose houses were demolished due to the ongoing house demolition campaign around Addis Ababa. EHRCO stated that the 3 experts who were assigned to investigate the matter and the Organization's driver as well as the company's car were arrested by the police and are being detained at a police station in the Alem Gena area. EHRCO also announced that it is being pressured and intimidated in relation to its work. This action is not only an action that prevents the organization from fulfilling the purpose of its establishment and the employees from maintaining their professional freedom.

Ethiopia has ratified the international and regional human rights instruments of the United Nations and the African Union. Article 29 - 31 of the FDRE Constitution clearly states freedom of speech, freedom of assembly, and the right to organize and hold peaceful demonstrations. Although the recently revised Civil Society Organizations Proclamation No. 1113/2019 has opened a new chapter for Civil Society Organizations working on advocacy in Ethiopia, the arrest of EHRCO professionals and the direct and indirect pressures observed on CSOs has left an unacceptable mark on the civic environment.

Ethiopia has the responsibility to respect and enforce the international and regional human rights agreements as well as the human rights protected by the Constitution and fulfill the conditions under which human rights are protected.

Therefore, we the undersigned CSOs strongly request that the arrested EHRCO workers be released immediately, and that the government bodies that carried out the arbitrary arrest be held accountable.

List of signatory Organizations of the Press Release:
1. Consortium of Ethiopian Human Rights Organizations (CEHRO)
2. Ethiopian Human Rights Council (EHRCO)
3. Center for Advancement of Rights and Democracy (CARD)
4. Lawyers for Human Rights (LHR)
5. Ethiopian Women Lawyers Association (EWLA)
6. Ethiopian Human Rights Defenders Center (EHRDC)
7. Union of Ethiopian Women and Children Associations (UEWCA)
8. Setaweet Movement
9. Inter Africa Group (IAG)
10. Association for Human Rights in Ethiopia (AHRE)
11. Women's Alliance for Peace and Social (WAPS)
12. Network of Ethiopian Women's Associations (NEWA)